(ሰኔ 27 ቀን 2014ዓ/ም አዲስ አበባ): የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ክብር አምባሳደር ብርቱካን አያኖ በቦሌ አለምአቀፍ አዉሮፕላን ማረፊያ በመገኝት ለእንግዶች አቀባበል አድርገዋል ።
ክብርት ሚኒስትር ድኤታ አምባሳደር ብርቱካን እንግዶችን እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት ፣ዲያስፖራዎች ስለ አገራቸዉ የተሞላ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ለማስቻል ፣በልማት ፣ በኢንቨስትመንት በአገር ገፅታ ግንባታ ዘርፍ እንዲሳተፉ፥
እንዲሁም በአገራቸው ጉዳይ ቀጥተኛ ተሳታፊ እንዲሆኑ ለማስቻል በዚህ ዓመት በርካታ ቁጥር ያላቸዉ ትዉልደ ኢትዮጵያዉያን ዲያስፖራዎች ወደ አገራቸዉ በመግባት ተሳትፎ ሲያደርጉ መቆየታቸዉን አስታዉሰዋል ።
 
የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ኤጀንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ክቡር ሙሃመድ እንድሪስ ( ዶ/ር ) በአቀባበሉ ላይ በመገኘት የሁለተኛው ዙር ከኢድ-እስከ- ኢድ አከባበር በይፍ ተጀምሯል እንግዶችም እየገቡ ነዉ ብለዋል ። መርሃ- ግብሩ በተለያዩ ስነ-ስርዓቶች በአዲስ አባባ አና በክልሎች እንደሚከበር ገልፀዎል።
 
የበደር ኢትዮጵያ አለምአቀፍ የሙስሊሞች ድርጅት ፕሬዝዳንት አቶ አህመድ ወርቁ የማህበሩ አባላት ጥሪዉን በመቀበል እና በቀጣይ ተሳትፎቸዉን ለማሳድ አዲስ አበባ መግባታቸዉን ተናግረዋል ።
በሰሜን አሜሪካ ነዋሪ በሆኑ ትዉልድ ኢትዮጵያዉያን የተመሰረተው በድር አለምአቀፍ የኢትዮጵያን ሙስሊሞች ድርጅት ከተመሰረተ ከ22 ዓመት በላይ አስቆጥሯል ።
በተመሳይ ከካናዳ እና በተለያዬ የዉጭ አገራት የሚገኙ የዲያስፖራ የአደረጃጀቶች ወደ አገራቸዉ ጥሪውን ተቀብዉ እየገቡ ይገኛሉ ።
 
ከተለያዩ ክፍለ አለማት የሚገኙ ኢትዮጵያ ከመጀመሪያው የኢድ በዓል አከባበር ጀምሮ ወደ አገራቸዉ በመግባት በተለያዬ መረሃ ግብሮች መሳተፋቸዉ ይታወሳል ።

Disclaimer: The official text of the Embassy Website is the English language version. Any discrepancies or differences created in translations are not binding and have no legal effect for compliance or enforcement purposes.

X
Twitter
Facebook
YouTube
Instagram